አዳማ
ከWikipedia
ኣዳማ በሌላ አጠራሩ ናዝሬት በኦሮሚያ ክልል ለኦሮሚያ በዋና ከተማነት የሚያገለግል የኢትዮጵያ ከተማ ነው። በምስራቅ ሸዋ ዞን በላቲቱድና ሎንጂቱድ 8.55° N 39.27° E ላይ ከአዲስ አበባ ወደ ደቡብ ምዕራብ 100 ኪሎመትር ላይ ይገኛል።
በማዕከላዊ ስታቲስቲስ ባለስልጣን ትመና የአዳማ ከትማ የ228,628 ሰው መኖሪያ ሲሆን እነሱም 114,255 ወንዶችና 114,368 ሴቶች ናቸው። ሌሎች ትመናዎችም አዳማ ከ200,000 ህዝብ በላይ መያዙን ያዘግባሉ። በ1986 የሕዝብ ቆጠራ አዳማ የ127,842 መኖሪያ ነበር።
አዳማ በትራንስፖርት ማእከልነት የታወቀ ከተማ ነው። ከተማው በአዲስ አበባና በድሬዳዋ መንገድ ላይ ይገኛል። አዲስ አበባ ጅቡቲና አሰብ (ከኢትዮ-እርትራ ጦርነት በፊት ኢትዮጵያ አሰብን ስትጠቀም) የሚመላሱ ቁጥራችው ከፍ ያሉ የጭነት መኪኖች የሚያልፉት በአዳማ ነው። ከአዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ የሚሄደው ምድር ባቡርም አዳማን ያቋርጣል።